ሰላምታ ለጉርዳ አባላት እና ደጋፊዎች በሙሉ በእየአላችሁበት፡፡
ደከመን ሰለቸን ሳትሉ፣ ጉርዳን በሀሳብ፣ በጉልበት እና በገንዘብ ስትደግፉ ለቆያችሁት የቦርድ አባላት እና፣ ለተቀራችሁትም አማካሪዎቻችን ሁሉ የአክብሮት ሰላምታዬ ይድረሳችሁ፡፡ ውድ ወገኖቼ ሆይ፤ ጉርዳ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ፣ ከጎናችን በመሆን፣ በሀገር ቤት በችግር የሚማቅቁ ወገኖቻችንን ለመርዳት ያደረጋችሁት ጥረት በእጅጉ የሚመሰገን ነው እና ከልብ አመሰግናችኋለሁኝ፡፡ የህዝባችን ችግር ግን፣ እጅግ ጥልቅ እና ስር የሰደደ በመሆኑ ገና ብዙ ይቀረናል፡፡ ችግሩን ነካካነው እንጂ አላጋመስነውም። ስለሆነም ለጉርዳ የገባነውን ቃል ለማሳካት፣ ከምንጊዜውም በበለጠ ተጠናክረን፣ ቃል ኪዳናችንን ጠብቀን፣ መስራቱ አማራጭ የሌለው ጎዳና በመሆኑ፣ አሁንም እንደ ቀድሞው ጠንክረን ለመስራት ተዘጋጅተናል። በእግዚአብሔር ፍቃድ እና፣ በእናንተ እገዛ፣ የተሻለ ደረጃ መድረስ እንደምንችል እርግጠኛ እየሆንኩ፣ እገዛችሁ እንዳይለየን አደራ እላለሁኝ። ተሾመ በስር አጨው የጉርዳ ሊቀ መንበር ጥር 3, 2012
1 Comment
Leave a Reply. |
Archives
January 2020
Categories |